የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ሁለተኛ የወዳጅነት ጨዋታውን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የወዳጅነት ጨዋታ ለማድረግ ወደ አሜሪካ ያቀናው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ሁለተኛ የወዳጅነት ጨዋታውን 4 ለ 2 አሸንፏል፡፡
ብሄራዊ ቡድኑ በዛሬው እለት ከሎደን ዩናይትድ ጋር ጨዋታውን አድርጎ ነው 4 ለ 2 ያሸነፈው፡፡
ጎሎችን ሱራፌል ዳኛቸው፣ሽመልስ በቀለ፣አስቻለው ታመነ እና ይሁን እንዳሻው ማስቆጠራቸውን ከኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ብሄራዊ ቡድኑ ቀደም ሲል የጋያና አቻውን 2 ለ 0 ማሸነፉ የሚታወስ ነው፡፡