Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያውያን የሚጠበቁበት የፍጻሜ ውድድር ይካሄዳል

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 14፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚጠበቁበት የ10 ሺህ ሜትር ወንዶች ፍጻሜ ውድድር ምሽት 1፡25 ላይ ይካሄዳል፡፡

በውድድሩ÷ አትሌት በሪሁ አረጋዊ፣ ሰለሞን ባረጋ እና ይስማው ድሉ ተጠባቂ ናቸው፡፡

በሌላ በኩል ቀን 12፡05 ላይ በሚካሄደው የሴቶች 1 ሺህ 500 ሜትር የግማሽ ፍጻሜ ውድድር÷ አትሌት ሂሩት መሸሻ፣ ድርቤ ወልተጂ እና ብርቄ ኃየሎም ተጠባቂ ናቸው፡፡

ትናንት በተካሄደው የ1 ሺህ 500 ሜትር ማጣሪያ÷ አትሌት ሂሩት መሸሻ 1ኛ፣ ድርቤ ወልተጂ 2ኛ እንዲሁም ብርቄ ኃየሎም 3ኛ ከየምድባቸው በመውጣት ለግማሽ ፍጻሜ ማለፋቸው ይታወቃል፡፡

19ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በሀንጋሪ ቡዳፔስት በመካሄድ ላይ ነው፡፡

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.