Fana: At a Speed of Life!

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን አዲስ አበባ ገባ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 23፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሀንጋሪ ቡዳፔስት በተካሄደው 19ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የተሳተፈወ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ አዲስ አበባ ገብቷል።

ልዑኩ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስም÷ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ፣ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ቀጄላ መርዳሳ፣ የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች አቀባበል አድርገውለታል።

በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮናው ኢትዮጵያ 2 የወርቅ፣ 4 የብርና 3 ነሐስ በድምሩ 9 ሜዳሊያዎችን ማግኘቷ ይታወቃል።

በሻምፒዮናው ኢትዮጵያ ከዓለም 6ኛ ከአፍሪካ ደግሞ 2ኛ ሆና ማጠናቀቋም የሚታወስ ነው።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.