በፕሪሚየር ሊጉ ባህር ዳር ከተማ ድል ቀንቶታል
አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 4 ፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ባህር ዳር ከተማ መቻልን 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡
ዛሬ 9 ሰዓት ባህር ዳር ከተማ እና መቻል ጨዋታቸውን ያደረጉ ሲሆን÷ ባህር ዳር ከተማ 2ለ 1 አሸንፏል፡፡
የባህር ዳር ከተማን የማሸነፊያ ጎሎች ፍሬው ሰለሞን እና ሀብታሙ ታደሰ አስቆጥረዋል፡፡
መቻልን ከሽንፈት ያልታደገችውን ጎል ደግሞ ሽመልስ በቀለ አስቆጥሯል፡፡
የፕሪሚየር ሊጉ ጨዋታ የሚቀጥል ሲሆን÷ ምሽት 12 ሰዓት ላይ ሻሸመኔ ከተማ ከሀዋሳ ከተማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡