Fana: At a Speed of Life!

የፕሪሚየር ሊጉ ሁለት መርሐ ግብሮች በአቻ ውጤት ተጠናቀቁ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሦስተኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ማጠቃለያ አዳማ ከተማ ከሀምበሪቾ ዱራሜ እንዲሁም ኢትጵያ ቡና ከባህር ዳር ከተማ 2 አቻ ተለያይተዋል፡፡

ለአዳማ ከተማ አብዲሳ ጀማል እና ዮሴፍ ታረቀኝ እንዲሁም ለሀምበሪቾ ዱራሜ በፍቃዱ አስረሳኸኝ እና ዳግም በፍቃዱ ጎሎችን አስቆጥረዋል፡፡

በውጤቱ መሰረት አዳማ ነጥቡን ወደ 5 ከፍ በማድረግ የነበረበትን 6ኛ ደረጃ ሲያስጠብቅ÷ ከሦስት ጨዋታዎች አንድ ነጥብ ብቻ ማግኘት የቻለው ሀምበሪቾ ዱራሜ 15ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡

እንዲሁም ጫላ ተሽታ እና ብሩክ በየነ ለኢትዮጵያ ቡና÷ ቸርነት ጉግሳ እና ፍፁም ጥላሁን ደግሞ ለባህዳር ከተማ ጎሎችን ማስቆጠር ችለዋል፡፡

ውጤቱን ተክትሎ ኢትዮጵያ ቡና በ7 ነጥብ 2ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ ባህርዳር ከተማ በነበረበት 7ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.