አትሌት ደሬሳ ገለታ በቤጂንግ ማራቶን ውድድር አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት ደሬሳ ገለታ እና አትሌት ይሁንልኝ አዳነ በቤጂንግ 2023 ማራቶን ውደድር አሸንፈዋል፡፡
አትሌት ደሬሳ ገለታ ርቀቱን 2 ሰዓት 7 ደቂቃ ከ41 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ ቀዳሚ መሆን ችሏል፡፡
ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ይሁንልኝ አዳነ ደግሞ ርቀቱን 2 ሰዓት 7 ደቂቃ ከ42 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በመጨረስ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል፡፡