Fana: At a Speed of Life!

በሹዙ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በቻይና ሹዙ በተካሄደ የማራቶን ውድድር በሁለቱም ጾታዎች ድል ቀንቷቸዋል፡፡

በወንዶች ምድብ አትሌት መልካ ደርቤ ርቀቱን 2 ሰዓት 14 ደቂቃ ከ23 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ ቀዳሚ መሆን ችሏል፡፡

በተመሳሳይ አትሌት ደራርቱ ሃይሉ በሴቶች ምድብ ርቀቱን 2 ሰዓት 27ደቂቃ ከ47 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ አሸንፋለች፡፡

አትሌቷ ከዚህ በፊት በቦታው ተይዞ የነበረውን ክብረ ወሰን ማሻሻል መቻሏንም ፒፕልስ ዴይሊ ኦንላይን ዘግቧል፡፡

በሹዙ 2023 የማራቶን ውድድር በአጠቃላይ ከ30 ሺህ በላይ አትሌቶች ተሳታፊ እንደነበሩ ተመላክቷል፡፡

#Ethiopia #China #Marathon

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.