Fana: At a Speed of Life!

በፕሪሚየር ሊጉ ሲዳማ ቡና እና ሀድያ ሆሳዕና ተጋጣሚዎቻቸውን ረቱ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ9ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሲዳማ ቡና እና ሀድያ ሆሳዕና ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል፡፡

9፡00 ላይ ኢትዮጵያ መድንን የገጠመው ሲዳማ ቡና በይገዙ ቦጋለ ብቸኛ ጎል 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

ውጤቱን ተከትሎም ሲዳማ ቡና ነጥቡን ወደ 11 ከፍ በማድረግ 7ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ÷ ኢትዮጵያ መድን ደግሞ በነበረበት 8ኛ ደረጃ ላይ ለመቆየት ተገዷል፡፡

በሌላ የጨዋታ መርሐ-ግብር 12፡00 ላይ አዳማ ከተማን የገጠመው ሀድያ ሆሳዕና በሰመረ ሀፍተይ ብቸኛ ጎል 1 ለ 0 ማሸነፍ ችሏል፡፡

ነብሮቹ ነጥባቸውን ወደ 11 ከፍ በማድረግ ከኢትጵያ ቡና፣ ወላይታ ድቻ እና ሲዳማ ቡና ጋር እኩል 7ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል፡፡

እንዲሁም አዳማ ከተማ በ13 ነጥቦች በነበረበት 5ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- FBC(Fana Broadcasting Corporate S.C.)
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.