Fana: At a Speed of Life!

በፕሪሚየር ሊጉ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክና አዳማ ከተማ ድል ቀናቸው

አዲስ አበባ፣ ጥር 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ12ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ዛሬ ሁለት ጨዋታዎች ተደርገዋል፡፡

ቀን 9 ሰዓት ላይ በተካሄደ ጨዋታ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባህር ዳር ከተማን 2 ለ 1 በማሸነፍ የሊጉን መሪነት አጠናክሯል፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን የማሸነፊያ ግቦች ቢንያም ጌታቸውና አዲስ ግደይ ሲያስቆጥሩ÷የባህር ዳር ከተማን ብቸኛ ግብ ደግሞ አለልኝ አዘነ አስቆጥሯል፡፡

በተመሳሳይ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በተካሄደ ጨዋታ አዳማ ከተማ ሃዋሳ ከተማን 3 ለ 2 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.