Fana: At a Speed of Life!

የአፍሪካ ዋንጫ የሩብ ፍፃሜ ጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ዛሬ ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ ጥር 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የሩብ ፍፃሜ ጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ናይጄሪያ ከአንጎላ እንዲሁም ዲሞክራቲክ ኮንጎ ከጊኒ ይገናኛሉ፡፡

ወደ ግማሽ ፍጻሜ ለማለፍ በሚደረገው ጨዋታ÷ ናይጄሪያ ከአንጎላ የሚያደርጉት ጨዋታ ምሽት 2፡00 ሠዓት ላይ በአቢጃን ፌኪክስ ሆፌት ስታዲየም ይደረጋል፡፡

ሁለቱ ቡድኖች በታሪክ 10 ጊዜ ተገናኝተው ናይጄሪያ በሦስቱ  እንዲሁም አንጎላ በሁለቱ ሲያሸንፉ÷ አምስቱን ጨዋታዎች ደግሞ አቻ ተለያይተዋል፡፡

በተመሳሳይ የጨዋታ መርሐ-ግብር ምሽት 5፡00 ሠዓት ላይ ዲሞክራቲክ ኮንጎ ከጊኒ በአላሳን ኦታራ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

ዲሞክራቲክ ኮንጎ ግብፅን እንዲሁም ጊኒ ደግሞ ጊኒ ቢሳውን በማሸነፍ ሩብ ፍፃሜውን መቀላቀላቸው ይታወቃል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.