Fana: At a Speed of Life!

15 ሰዎችን ጭኖ የነበረ የሩሲያ ወታደራዊ አውሮፕላን ተከሰከሰ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) 15 ሰዎችን ጭኖ የነበረ የሩሲያ ወታደራዊ መጓጓዣ አውሮፕላን መከስከሱ ተነገረ።

አውሮፕላኑ ከሞስኮ ሰሜን ምስራቅ አቅጣጫ በኢቫኖቫ ክልል አየር ላይ እያለ በእሳት ከተያያዘ በኋላ የመከስከስ አደጋ እንዳጋጠመው ተገልጿል።

አይኤል-76 የተሰኘው አውሮፕላን በውስጡ ስምንት የበረራ ሰራተኞችና ሰባት ተጓዦችን ይዞ እንደነበረ የተገለጸ ሲሆን÷ አንደኛው የሞተር ክፍሉ በእሳት ተያይዞና ከባድ የሆነ ጥቁር ጭስ ማውጣቱ በማህበራዊ ሚዲያ የወጡ ምስሎች አመላክተዋል።

የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አደጋው ማጋጠሙን ያረጋገጠ ቢሆንም ስለደረሰው ጉዳት ያለው ነገር አለመኖሩን ዲፌንስ ብሎግ ዘግቧል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.