Fana: At a Speed of Life!

ራፋኤል ቤኒቴዝ ከሴልታ ቪጎ አሰልጣኝነታቸው ተሰናበቱ

 

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ራፋኤል ቤኒቴዝ ከስፔኑ ሴልታ ቪጎ ቡድን አሰልጣኝነታቸው ተሰናብተዋል፡፡

የሊቨርፑልና የቼልሲ የቀድሞ አሰልጣኝ የነበሩት ቤኒቴዝ የላሊጋውን ቡድን በአሰልጣኝነት የተረከቡት ባለፈው ሰኔ ወር ነበር፡፡

ሴልታ ቪጎ በራፋኤል ቤኒቴዝ አሰልጣኝነት ወቅት ካደረጋቸው 28 የላሊጋ ጨዋታዎች ውስጥ ማሸነፍ የቻለው 5ቱን ብቻ ነው፡፡

ሴልታ ቪጎ በላሊጋው የደረጃ ሰንጠረዥ በ24 ነጥብ በ17ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.