Fana: At a Speed of Life!

በመዲናዋ 19 ጤና ጣቢያዎች የቀዶ ሕክምና የማዋለድ አገልግሎት እየሰጡ ነው

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ19 ጤና ጣቢያዎች የሚሰጠው የቀዶ ሕክምና የማዋለድ አገልግሎት የእናቶችና ሕጻናትን ጤና በመጠበቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ጤና ቢሮ ገለጸ።

የቢሮው የእናቶችና ሕጻናት ጤና ዳይሬክተር ስንዱ መኩሪያ÷ የሕክምና አገልግሎቱ በሆስፒታሎች ላይ ያለውን ጫና ከመቀነስ ባሻገር የእናቶችና የሕጻናት ጤና በመጠበቅ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ ነው ብለዋል፡፡

በቀጣይም ጤና ጣቢያዎችን በማዘመን ሆስፒታሎች የሚሰጡትን ሌሎች አገልግሎቶች ጤና ጣቢያዎች እንዲጀምሩ የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ለኢዜአ ተናግረዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.