Fana: At a Speed of Life!

በአዳባ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ7 ሰዎች ሕይወት አለፈ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 19፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በምዕራብ አርሲ ዞን አዳባ ወረዳ ኤጀርሳ ቀበሌ ትናንት ምሽት 2 ሰዓት አካባቢ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሰባት ሰዎች ሕይወት አለፈ።

የምዕራብ አርሲ ዞን ትራፊክ ክፍል ሃላፊ ኮማንደር ከማል አማን እንዳሉት፤ አደጋው የደረሰው ከጉብሳ ወደ አዳባ እህል ጭኖ ሲጓዝ የነበረ ከባድ ተሽከርካሪ ፍሬን በጥሶ በመገልበጡ ነው።

በአደጋው ሹፌሩ፣ ረዳቱን እና ከላይ ተሳፍረው የነበሩ ሰዎችን ጨምሮ የሰባት ሰዎች ሕይወት ማለፉን ተናግረዋል።

በሁለት ሰዎች ላይም ከባድ ጉዳት እንደደረሰ ሃላፊው ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል።

በመላኩ ገድፍ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.