በኅብረተሰቡ ውስጥ የሴቶች ሚና ብዙ መልክና ገፅ ያለው ነው – ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር)
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 19፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኅብረተሰቡ ውስጥ የሴቶች ሚና ብዙ መልክና ብዙ ገፅ ያለው ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት÷ “በዛሬው ውይይት ከተለያየ የማኅበረሰብ ዳራ የተውጣጡ ከመላው ኢትዮጵያ የመጡ ሴቶችን ሀሳብ አዳምጫለሁ” ብለዋል፡፡
በኅብረተሰቡ ውስጥ የሴቶች ሚና ብዙ መልክ እና ብዙ ገፅ ያለው መሆኑንም በመልዕክታቸው አመላክተዋል።