Fana: At a Speed of Life!

ለሰላም ማስከበር ተልዕኮ በደቡብ ሱዳን ለሚሰማሩ ከፍተኛ መኮንኖች ሽኝት ተደረገ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ለሰላም ማስከበር ተልዕኮ በደቡብ ሱዳን ለሚሰማሩ የኢትዮጵያ ፖሊስ ከፍተኛ መኮንኖች ሽኝት ተደርጓል።

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል በሽኝት ፕሮግራሙ ላይ እንደገለጹት÷የኢትዮጵያ ፖሊስ ሠራዊት በሥነ-ምግባሩ እና በወታደራዊ አቅሙ በዓለም አቀፍ ተቋማት ተፈላጊ እና ተመራጭ እየሆነ መጥቷል፡፡

የፖሊስ መኮንኖቹ በስምሪታቸው የኢትዮጵያ ፖሊስ አሁን የደረሰበትን ደረጃ የሚያመላክት የላቀ ሥነ-ምግባርና ፖሊሳዊ ሙያ ሊያሳዩ እንደሚገባ ማስገንዘባቸውንም የፌዴራል ፖሊስ መረጃ ያመላክታል።

መሰል ዓለም አቀፍ ተሳትፎ የሚጠይቁ ሥራዎች ይበልጥ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ጠቁመው÷ ለሰላም አስከባሪ ተጓዦች ተልዕኳቸው የተሳካ እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።

የፌደራል ፖሊስ ሰላም ማስከበር ማዕከል ሃላፊ ኮማንደር ተገኝ አጋዥ በበኩላቸው ÷ በሱዳን፣ በደቡብ ሱዳንና በአብዬ ግዛቶች እንዲሁም በሐይቲ የተሰማሩ የፌደራል ፖሊስና የክልል ፖሊስ አመራሮች የተሰጣቸውን ግዳጅ በብቃት በመወጣት የሀገራቸውንና የተቋማቸውን መልካም ገጽታ መገምባታቸውን ተናግረዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.