Fana: At a Speed of Life!

ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) የቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን ድጋፍ ለኢትዮጵያ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽዖ እንዳለው ገለጹ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን የሚሰጠው ድጋፍ ለኢትዮጵያ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽዖ እንዳለው ገለጹ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ የቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ከሆኑት ማርክ ሱዝማን እና ቡድናቸው ጋር መወያታቸውን ጠቅሰው፤ በዚህም ደስታ እንደተሰማቸው በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ገልጸዋል፡፡

የቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን በግብርና፣ ጤና፣ በሥርዓተ-ምግብ፣ በአካታች የፋይናንስ ሥርዓት እና በሌሎች ዘርፎች የሚሰጠው ጠቃሚ ድጋፍ ለኢትዮጵያ ዕድገት ከፍ ያለ አስተዋጽዖ እንዳለውም ጠቅሰዋል፡፡

ይህን ትብብር በማላቅ እና በአዳዲስ ዘርፎች በመተባበር እንሰራለን ሲሉም አረጋግጠዋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.