Fana: At a Speed of Life!

በአብዬ ደቡባዊ ሴክተር በሰላም ማስከበር ግዳጅ ላይ የተሰማራው የ24ኛ ሞተራይዝድ ሰላም አስከባሪ ሻለቃ አባላት የጁንታውን ድርጊት አወገዙ

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 10 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአብዬ ደቡባዊ ሴክተር በሰላም ማስከበር ግዳጅ ላይ የተሰማራው የ24ኛ ሞተራይዝድ ሰላም አስከባሪ ሻለቃ አባላት የህውሓት ጁንታውን ድርጊት አወገዙ ።
የሻለቃው ዋና አዛዥ ኮሎኔል መብረሀቶም ሀይሉ ÷ ከሀዲው የህውሀት ቡድን በሰሜን ዕዝ የሠራዊት አባላት ላይ የፈፀመው ዘግናኝና ድርጊት ሊወገዝ ይገባዋል ብለዋል ።
በቀጣይም የተጀመረውን የህግ ማስከበር ተግባር በመደገፍና ውስጣዊ አንድነታችንን በማጠናከር ግዳጃችንን ያለምንም መደናገጥ አጠናክረን እናስቀጥላለን ማለታቸውን ከኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.