Fana: At a Speed of Life!

የፖለቲካ ፓርቲዎች በ160 የምርጫ ክልሎች ቅሬታ አቅርበዋል-ቦርዱ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 22 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የፖለቲካ ፓርቲዎች በ160 የምርጫ ክልሎች ቅሬታ ማቅረባቸውን የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ፡፡
የቦርዱ ሰብሳቢ ወይዘሪት ብርትኳን ሚደቅሳ ለጋዜጠኞች መግለጫ እየሰጡ ነው፡፡
በመግለጫቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች ቅሬታ የመጨረሻ ውጤትን ሊያዘገየው ይችላል የሚል ስጋት እንዳለ የገለፁ ሲሆን ፓርቲዎቹ በ160 የምርጫ ክልሎች ቅሬታ ማቅረባቸውን ተናግረው፡፡
ቦርዱም ቅሬታዎቹ በፍጥነት መፍታት ይኖርበታል ብለዋል፡፡
በማጣራት ሂደቱም የምርጫውን ውጤት ሊለውጡ የሚችሉ ቅሬታዎች ካሉ በድጋሚ ምርጫ የምናካሂድባቸው ክልሎች ሊኖሩ እንደሚችሉ በህጉ መሰረት እናውቃለን ነው ያሉት ሰብሳቢዋ፡፡
በሌላ በኩልም 942 የምርጫ ውጤት ሰነዶችን ቦርዱ እያረጋገጠ ለህዝቡ እንደሚያቀርብ ገልፀዋል፡፡
እስካሁንም 618 የሚሆኑ የምርጫ ውጤት ሰነዶች ወደ ማዕከል መጥተዋል ነው ያሉት፡፡
በፌቨን ቢሻው
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.