Fana: At a Speed of Life!

ትምህርት ሚኒስቴር አንድ ኢንተርናሽናል ትምህርት ቤት አገደ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 3፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) ትምህርት ሚኒስቴር የዓለም አቀፍና የማህበረሰብ ትምህርት ቤቶች ፈቃድ አሰጣጥና ዕድሳት መመሪያን መሰረት አድርጎ ስኩል ኦፍ ኔሽን ትምህርት ቤት ላይ እገዳ መጣሉን አስታውቋል፡፡

አዲሱ የትምህርት ዘመን ከመጀመሩ በፊት በትምህርት ክፍያ ጭማሪ ዙሪያ በተደጋጋሚ ከወላጆች ቅሬታ በመቅረቡ የትምህርት ሚኒስቴር የዘርፍ አመራሮችና የባለሙያዎች ቡድን ትምህርት ቤቱንና የወላጅ ኮሚቴውን በማወያየት ከስምምነት ላይ እንዲደርሱ በተደጋጋሚ ጊዜ ድጋፍ ሲያደርግ ቆይቷል ነው የተባለው፡፡

ቢሆንም በተደረጉት ውይይቶች ስምምነት ላይ መድረስ ባለመቻሉ ትምህርት ቤቱ ከዛሬ ጀምሮ ትምህርት ሚኒስቴር ባወጣው መመሪያ መሰረት ከወላጅ ኮሚቴ ጋር ፈጥኖ በመነጋገር ምንም አይነት የትምህርት ስራ እንዳይሰራ ታግዷል መባሉን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.