Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

በኔዘርላንድስ ግማሽ ማራቶን አትሌት ፀሃይ ገመቹ አሸናፊ ሆናለች

አዲስ አበባ፣ ጥር 4፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኔዘርላንድስ በተካሄደ የሴቶች ግማሽ ማራቶን ሩጫ ውድድር አትሌት ፀሃይ ገመቹ አሸናፊ ሆናለች። አትሌት ፀሃይ ርቀቱን 1 ሰዓት ከ20 ደቂቃ ከ29 ሰከንድ በሆነ ጊዜ በመግባት ስታሸንፍ፥ አትሌት ታደለች በቀለ ሶስተኛ በመሆን አጠናቃለች። በተመሳሳይ በስፔኑ ሁዋን ሙጉዬርዛ አመታዊ የግማሽ ማራቶ ውድድር አትሌት ታደሰ ወርቁ በወንዶች ምድብ አሸናፊ ሆኗል። አትሌት ታደሰ ርቀቱን 31 ደቂቃ ከ39 ሰከንድ በሆነ ጊዜ በመግባት ነው ያሸነፈው። በሌላ በኩል በአዲስ አበባ የ10 ኪሎ ሜትር የሩጫ…
Read More...

የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 8ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በተለያዩ ከተሞች ተካሂደዋል

አዲስ አበባ፣ ጥር 03፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 8ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በዛሬው ዕለት በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች ተካሂደዋል። በዚህም ወልቂጤ ከተማን ከሜዳው ውጭ የገጠመው የአምናው ሻምፕዮን መቀሌ 70 እንደርታ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የሊጉን መሪነት ተረክቧል በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ቡናን በሜዳው ያስተናገደው ፋሲል ከነማ 2ለ1 በሆነ ውጤት…

የሀላባን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ የሩጫ ውድድር ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ጥር 2፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሀላባን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ የ8 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር በሀላባ ቁሊቶ ከተማ ተካሄደ። “ሴራችን ለሰላማችን” በሚል ሀሳብ በተካሄደው የሩጫ ውድድር ላይ የአካባቢው ነዋሪዎች ተሳትፈዋል። ውድድሩን ያስጀመረችው አትሌት ፋንቱ ምጌሶ “ሰላም ለሁሉም ነገር መሠረት በመሆኑ የሀላባ ብሄር የዘመን መለወጫ…

በቶኪዮ ኦሊምፒክ ፖለቲካዊ ይዘት ያላቸውን መልዕክቶች ማስተላለፍ እንደማይቻል ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ጥር 1፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በ2020 ቶኪዮ ኦሊምፒክ ላይ የእጅ ምልክትን ጨምሮ ፖለቲካዊ ይዘት ያላቸውን መልዕክቶች ማስተላለፍ እንደማይቻል ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ አስታወቀ። ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በቀጣዩ ሃምሌ ወር በጃፓን ቶኪዮ በሚካሄደው ኦሊምፒክ ውድድር ላይ ለተወዳዳሪ አትሌቶች በተከለከሉ የደስታ አገላለጾች እና የሚያስተላልፏቸውን መልዕክቶች…

በፕሪምየር ሊጉ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ መሪነቱን ተረከበ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 29፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 7ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በዛሬው ዕለት በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች ተካሂደዋል። ሁለተኛ ደረጃ ላይ የነበረው ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ወደ ድሬዳዋ በማቅናት 2 ለ 0 ማሸነፍ ችሏል፡፡ በሌላ ጨዋታ መሪው ፋሲል ከነማ ወደ ሶዶ በማቅናት ከወላይታ ዲቻ ጋር ያደረገውን ጨዋታ 1 ለ 1 በማጠናቀቁ ቢጫ…

የሴኔጋልና የሊቨርፑሉ አጥቂ ሳዲዮ ማኔ የአፍሪካ የዓመቱ ኮኮብ ተጫዋች ሆነ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 29፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሴኔጋል ብሄራዊ ቡድን እና የሊቨርፑሉ አጥቂ ሳዲዮ ማኔ በአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) የአፍሪካ የዓመቱ ኮኮብ ተጫዋች ሆኖ ተመረጠ፡፡ ሳዲዮ ማኔ የዓመቱ ኮኮብ ተጫዋችነት ሽልማትን ያገኘነው የቡድን አጋሩን ሞሃመድ ሳላህ እና የአልጀሪያና የማንቼስተር ሲቲውን የመስመር ተጫዋች ሪያድ ማህሬዝን አስከትሎ ነው።…

በቻይና በተካሄደ የማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱ ጾታዎች አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 27፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በሳምንቱ መጨረሻ በተለያዩ የዓለማችን ክፍሎች በተካሄዱ ውድድሮች ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀንቷቸዋል። በቻይና በተደረገው የማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያኑ ሲያሸንፉ በሴቶች ምድብ ከ1ኛ እስከ 8ኛ ያለውን ደረጃ በመያዝ አጠናቀዋል። በውድድሩ በወንዶች አትሌት ብርሃን ንባባው ርቀቱን በ2 ሰዓት ከ8 ደቂቃ ከ16 ሰከንድ…