Fana: At a Speed of Life!

በአፍሪካ የመሪዎች ጉባዔ የተሳተፉ የተለያዩ ሀገራት መሪዎች ወደ ሀገራቸው ተሸኙ

 

አዲስ አበባ፣ የካቲት 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የ36ኛው የአፍሪካ የመሪዎች ጉባዔ መጠናቀቅን ተከትሎ የተለያዩ ሀገራት መሪዎች ወደ ሀገራቸው ተሸኝተዋል፡፡

በዚህ መሰረትም የኬንያ፣ ሴኔጋል ፣ ሩዋንዳ፣ ሞሮኮ፣ ማዳጋስካር፣ አልጄሪያ፣ ኮንጎ፣ ደቡብ አፍሪካ ፣ቻድ ፣ጋና ቦትስዋና፣ ናይጄሪያ፣ ሶማሊያ፣ ሲሸልስ እና ብሩንዲ መሪዎች ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡

በተጨማሪም የሌሴቶ፣ አንጎላ፣ ጋቦን፣ ጅቡቲ፣ ኒጀር፣ ኮንጎ ብራዛቪል፣ ፍልስጤም እና የሴራሊዮን መሪዎች ወደ ሀገራቸው ማቅናታቸው ተገልጿል፡፡

የኢትዮጵያ የተለያዩ ሚኒስትሮችም ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በመገኘት አሸኛኘት አድርገውላቸዋል፡፡

ቀሪዎቹ መሪዎችም ዛሬ ማምሻውን ወደ ሀገራቸው ይመለሳሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.