Fana: At a Speed of Life!

በደቡብ አፍሪካ ስዌቶ የወጣቶች እንቅስቃሴ መሪ ሎንታታ ላክስ አዲስ አበባ ገባ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 25፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ አፍሪካ ስዌቶ የወጣቶች እንቅስቃሴ መሪ ሎንታታ ላክስ ዛሬ ማለዳ አዲስ አበባ ገባ።

የፓን አፍሪካኒዝም አቀንቀኙ ወጣቱ ላክስ ወደ ኢትዮጵያ የመጣው #የበቃ እንቅስቃሴ በኢትዮጵያ ብቻ ተገድቦ እንዳይቀርና ዘላቂነት እንዲኖረው ለማድረግና ያለውን ልምድ ለማካፈል ነው።

ላክስ በተለይ አፍሪካዊያን ወጣቶች የውጭ ጫናዎችን እንዴት መቋቋም እንዳለባቸውና ባዕድ ሀሳብ እንዳይገዛቸው የሚታገል ወጣት ነው።

ወጣቱ በደቡብ አፍሪካ ወጣቶችና የተለያዩ ተቋማት ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነት ያለው ሲሆን ‘የአፍሪካውያን ችግር በአፍሪካውያን መፈታት አለበት’ የሚል ጽኑ አቋም አለው።

ላክስ ወደሚወዳት የአፍሪካ እናት ኢትዮጵያ በመምጣቱ የተሰማውን ደስታ ገልጿል።

ላክስ በቦሌ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርስ የጠቅላይሚኒስትር ጽህፈት ቤት ተወካይ ረዳት ፕሮፌሰር ነብዩ ባዬ እና የኢትዮጵያ ወጣቶች ፌዴሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት ፅጌሬዳ ዘውዱ ተቀብለውታል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.