Fana: At a Speed of Life!

በሩብ ዓመቱ 2 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር የሚገመቱ የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ተያዙ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 22፣2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የጉምሩክ ኮሚሽን በ2015 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት 2 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎችን መያዙን አስታወቀ።

የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን፣ የፌደራል ፖሊስ፣ገቢዎች ሚኒስቴር እና ፍትህ ሚኒስቴር የ2015 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት የኮንትሮባንድ መከላከል ዕቅድ አፈጻጸምን እየገመገሙ ነው።

በጉምሩክ ኮሚሽን የኢንተለጀንስ ዳይሬክተር ተገኔ ደረሰ እንዳሉት÷ የኮንትሮባንድ ወጪና ገቢ ዕቃዎችን ለመቆጣጠር የተለያዩ እርምጃዎች ተወስደዋል።

በዚህም በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ግምታዊ ዋጋቸው 2 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር የሚሆኑ የተለያዩ የኮንትሮባንድ እቃዎች እንደተያዙ መናገራቸውን ኢዜአ ዘገቧል፡፡

በኮንትሮባንድ ተግባር የተሳተፉ 351 ግለሰቦችን በህግ ቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉንም ነው ዳይሬክተሩ ያነሱት።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.