Fana: At a Speed of Life!

በቦረና ዞን ድርቁን ተከትሎ ከ7 ሺህ 800 በላይ ተማሪዎች ትምህርት አቋረጡ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 17፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)በቦረና ዞን ድርቁን ተከትሎ ከ7 ሺህ 800 በላይ ተማሪዎች ትምህርታቸውን ማቋረጣቸውን የቦረና ዞን ትምህርት ጽኅፈት ቤት ገለፀ።

የፅህፈት ቤቱ ሃላፊ ተስፋዬ ወ/ሚካኤል እንደገለፁት÷ በዞኑ ባሉ 490 ትምህርት ቤቶች በመማር ላይ የሚገኙ የ174 ሺህ ተማሪዎች ውጤትም ቀንሷል።

ተማሪዎቹን ከትምህርት ገበታቸው እንዳይቀሩ የምገባ ፕሮግራም እየተደረገ እንዳለ የገለፁ ሲሆን÷ምገባውን ለማስቀጠል ክልሉ ወደ 45 ሚሊየን ብር መመደቡን አመላክተዋል።

አሁን ላይ በ80 ትምህርት ቤቶች የመማሪያ፣ የማደሪያ እና የምገባ አገልግሎት እየተሰጠ እንደሚገኝ ተገልጿል፡፡

በዞኑ ድርቁን ተከትሎ በተስተዋለው ከባድ ንፋስ 47 ትምህርት ቤቶች መፍረሳቸው ገልፀው ለመልሶ ግንባታም የክልሉ መንግስት 5 ሚሊየን ብር መድቧል ነው ያሉት፡፡

21 ትምህርት ቤቶችም በፍጥነት እንዲገነቡ እንቅስቃሴ ተጀምሯል ተብሏል።

እስካሁን ድርቁን ተከትሎ የተዘጉ ትምህርት ቤቶች የሉም ያሉት ሃላፊው በፈረሱት ቦታ ዳስ ተጥሎ እንዲማሩ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።

በታሪኩ ለገሰ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.