Fana: At a Speed of Life!

በፕሪሚየር ሊጉ መቻል ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ23ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ሁለት ጨዋታዎች ተካሂደዋል፡፡

ቀን 9 ሰዓት ላይ በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደ ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡

የመቻልን ብቸኛ ግብ የአማካይ ተጫዋቹ ከነዓን ማርክነህ 62ኛው ደቂቃ ላይ በፍጹም ቅጣት ምት አስቆጥሯል፡፡

ይህን ተከትሎም የሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ በውድድር ዓመቱ ለሁለተኛ ጊዜ ሽንፈተን አስተናግዷል።

በተመሳሳይ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በተደረገ ጨዋታ ወልቂጤ ከተማ ለገጣፎ ለገዳዲን 3 ለ 2 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.