ሽመልስ በቀለ መቻልን ተቀላቀለ
አዲስ አበባ፣ ጷጉሜን 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ከሀገር ውጭ በተለያዩ ሀገራት ክለቦቸ ለ10 ዓመታት ሲጫወት የቆየው ሽመልስ በቀለ ለመቻል ፈርሟል፡፡
የብሄራዊ ቡድኑ ቁልፍ ተጫዋች ከዘጠኝ ዓመታት በፊት ወደ ግብፅ ያመራ ሲሆን÷ በግብፅ ለሚገኙ ሶስት የተለያዩ ክለቦች መጫዎች ችሏል፡፡
በፔትሮጀት ስድስት ዓመታትን፣በምስሪ ላል መቃሳ ሁለት ዓመታትን በኤል ጎውና ለአንድ ያመት ያህል በተመሳሳይ በኢ ኤን ፒ ፒ አይ አንድ ዓመት ማሳለፍ ችሏል፡፡
ቀሪ አንድ አመት ኮንትራት እየቀረው ከኢ ኤን ፒ ፒ አይ የተለያየው ሽመልስ ወደ ሀገር ቤት በመመለስ በዛሬው እለት በሁለት ዓመት ውል መቻልን መቀላቀሉን ሶከር ኢትጵያ ዘግቧል፡፡