Fana: At a Speed of Life!

የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ያሰለጠኗቸውን ተማሪዎች እያስመረቁ ነው

አዲስ አበባ፣ የካቲት 16፣ 2016 (ኤፍ ቢ) ወለጋ፣ አርሲ እና ዲላ ዩኒቨርሲቲዎች በመደበኛ እና በተከታታይ የትምህርት መርሀ ግብር በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ ያሰለጠነኗቸውን ተማሪዎች እያስመቁ ነው።

 
ወለጋ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያ ፣ በሁለተኛ ድግሪ እና በፒ ኤች ዲ ያሰለጠናቸውን 1ሺህ 374 ተማሪዎች እያስመረቀ ነው ፡፡
 
በምረቃ ስነ-ስርዓቱ የወለጋ ዩኒቨርሲቲ የሴኔት አባላት ፣ የተመራቂ ወላጆች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
 
በተመሳሳይም አርሲ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንሰ ኮሌጅ በተለያዩ መሰኮች ያሰለጠናቸውን 214 ተማሪዎች አስመርቋል።
 
በምረቃ መርሃ ግብሩ የጤና ሳይንስ ኮሌጁ ዲን ዶ/ር ዲዳ ባቱ ፣ኮሚሸነር ደራርቱ ቱሉ ፣የተመራቂ ወላጆች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
 
እንዲሁም የዲላ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ሲያስምራቸው የቆዩ 434 ተማሪዎችን እያስመረቀ ነው፡፡
 
በገላና ተስፋ፣ኦሊያድ በዳኔ እና ሂርጶ ሺቦ
 
 
#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.