Fana: At a Speed of Life!

ሶስት ሀገር በቀል ኩባንያዎች የመልቲ ሞዳል ትራንስፖርት አገልግሎት ፈቃድ አገኙ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 4፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ሶስት ሀገር በቀል ኩባንያዎች መልቲ ሞዳል ትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችላቸውን ፈቃድ አገኙ።

ድርጅቶቹ የብቃት ማረጋገጫ እውቅና የምስክር ወረቀት ከትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) እጅ ተቀብለዋል።

ፓናፍሪክ ግልባል ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር፣ ጥቁር አባይና ኮስሞስ መልቲ ሞዳል ሼር ካምፓኒ የመወዳደሪያ መስፈርቱን አሟልተው የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሰጡ ፈቃድ የተሰጣቸው ድርጅቶች ናቸው።

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) እንደተናገሩት÷ የኢትዮጵያን ሎጂስቲክስ አገልግሎት ተወዳዳሪ ለማድረግ የግሉ ዘርፍ ድርሻ ከፍተኛ ነው።

የግል ድርጅቶች የሎጂስቲክስ አገልግሎት እንዲሰጡ የግሉን ዘርፍ የሚያሳትፍ መመሪያ መዘጋጀቱን ጠቁመው÷ በመመሪያው መሰረት ለግል ትራንስፖርት ሰጪ ድርጅቶች ፈቃድ መሰጠት መጀመሩን ገልፀዋል።

ዕውቅና እና ፈቃድ የተሰጣቸው ድርጅቶችም ሃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ማሳሰባቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.