Fana: At a Speed of Life!

ምክር ቤቱ የዒድ አል-ፈጥር በዓልን በማስመልከት የእንኳን አደረሣችሁ መልዕክት አስተላለፈ

 

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 1ሺህ 445ኛውን የዒድ አል-ፈጥር በዓልን በማስመልከት ለሕዝበ ሙስሊሙ የእንኳን አደረሣችሁ መልዕክት አስተላልፏል።

በመልዕክቱ ÷ የዒድ አል-ፈጥር በዓል የሠላም የመረዳዳትና የመተሳሰብ መገለጫ ሆኖ እንዲያልፍ መልካም ምኞቱን ገልጿል ።

ሕዝበ ሙስሊሙ ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ወገኖቹ ጋር በመሆን የኢትዮጵያን ሠላምና አንድነት ለማፅናት የዜጎችን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለመረጋገጥ እያበረከተ ያለውን ዘርፈ ብዙ አስተዋጽዖ አጠናክሮ እንዲቀጥልም ምክር ቤቱ አሳስቧል ።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.