Fana: At a Speed of Life!

ለአርብቶ አደሩ የጤና ፍላጎት ምላሽ የሚሰጥ ፕሮጀክት ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ35 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ለሚቀጥሉት 5 ዓመታት የሚተገበርና ለአርብቶ አደሩ የጤና ፍላጎት ምላሽ የሚሰጥ ፕሮጀክት ይፋ ሆነ።

ፕሮጀክቱ በ4 ክልሎች ውስጥ የሚገኙ 35 የአርብቶ አደር ወረዳዎችን ያቀፈ መሆኑ ተገልጿል።

በስነ ተዋልዶ ጤና፣ በስርዓተ ምግብ፣ የእናቶች እና የህፃናት፣ የአፍላ ወጣቶች ጤና፣ የጨቅላ ህፃናት ጤና እንዲሁም የቤተሰብ ዕቅድን ማዕከል ያደረገው የዚህ ፕሮጀክት የማስጀመሪያ መርሐ ግብር መካሄዱን የጤና ሚኒስቴር መረጃ አመልክቷል።

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ፕሮጀክቱ እውን እንዲሆን ላደረጉ አካላት ምስጋና አቅርበው፤ የአርብቶ አደር ማህበረሰብ ጤናው ተጠበቆ እንዲኖር የሚመለከታቸው አካላት ከሚኒስቴሩ ጎን ጥሪ አቅርበዋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.