የኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ (ኦ ቢ ኤን) ሆርን ኦፍ አፍሪካ ቻናል ተመረቀ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ)ጠቅላይ ሚነስትር ዐቢይ አሕመድ የኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ (ኦ ቢ ኤን) ሆርን ኦፍ አፍሪካ ቻናል እና የኦቢቫን ዘመናዊ ኤችዲ (HD) ተንቀሳቃሽ ማሰራጫን መርቀዋል፡፡
በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ እና ሌሎች የፌደራል እና የክልል ርዕሰ መስተዳድሮች ተገኝተዋል፡፡
በተያያዘ የወሊሶ፣ አምቦ፣ እና ባሌ ሮቤ ኤፍ ኤም ሬዲዮ ጣቢያዎች በዛሬው ዕለት ተመርቀዋል፡፡