ጠ/ሚ ዶ/ር አብይና ፕሬዚዳንት ኢሳያስ የአዳማ የኢንዱሰትሪ ፓርክን ጎበኙ
በታያየዘ ዜና ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ እና የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በቢሾፍቱ ከተማ የሚገኘውን የሆላንድ የእንሰሳት እርባታ እና የወተት ተዋፅኦ ማቀነባበሪያንም ጎብኝተዋል።
ማቀነባበሪያው ራሱ ከሚያረባቸው እና በአከባቢው ከሚገኙ አርሶ አደሮች ከሚሰበስበው የወተት ምርት የተለያዩ የወተት ተዋፅኦዎችን በማምረት የሚታወቅ ነው።
ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ትናንት ነበር ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ የገቡት።