Fana: At a Speed of Life!

19 ሺህ 739 ጥይቶችን ወደ ባህርዳር ሊያስገቡ የሞከሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 26 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) 19 ሺህ 739 ተተኳሽ ጥይቶችን በባለ ሶስት እግር ባጃጅ ተሽከርካሪ ጭነው ወደ ባህር ዳር ሊያስገቡ የሞከሩ ሁለት ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን በጉምሩክ ኮሚሽን የባህር ዳር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

የቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቱ ስራ አስኪያጅ አቶ አለነ መሀሪ ለኢዜአ እንደገለጹት ግለሰቦቹ የቱርክ ሰራሽ ሽጉጥ ጥይቶቹን ከምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ ከደለጎ ከተማ ወደ ባህር ዳር ለማስገባት ሲሞክሩ ትናንት ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት በቁጥጥር ስር ውለዋል።

ግለሰቦቹ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 1-43622 አ.ማ በሆነ በባለ ሶስት እግር ባጃጅ ተሽከርካሪ ጭነው ወደ ባህርዳር ለማስገባት ሲሞክሩ በሻውራ ጉምሩክ ሰራተኞችና በፌደራል ፖሊስ ትብብር በተደረገ የኬላ ፍተሻ መያዛቸውን ተናግረዋል።

ተጠርጣሪ ግለሰቦቹ ለፖሊስ ተላልፈው ተሰጥተው ጉዳዩ እንዲጣራ እየተደረገ መሆኑንም አመላክተዋል።

ህገ ወጥ እንቅስቃሴ የማህበረሰቡንም ሆነ የሃገሪቱን ሰላም የሚጎዳ በመሆኑ ህብረተሰቡ መሰል ወንጀሎች ሲያጋጥሙት ለሚመለከተው አካል በማሳወቅ ሀላፊነቱን እንዲወጣ ስራ አስኪያጁ ጥሪ አቅርበዋል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.