Fana: At a Speed of Life!

በምስራቅ ሸዋ ዞን የምርጫ ቁሳቁስ ስርጭት እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 12 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በምስራቅ ሸዋ ዞን በምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ቁሳቁስ ስርጭት እየተካሄደ ነው።

ስርጭቱ በዞኑ ድምፅ በሚሰጥባቸው 11 የምርጫ ክልሎችና 1 ሺህ 540 የምርጫ ጣቢያዎች ነው እየተካሄደ መሆኑን የምስራቅ ሸዋ ዞን የምርጫ ፅህፈት ቤት አስተባባሪ አቶ ደበሌ ወርቁ ተናግረዋል።

አክለውም የቁሳቁስ ስርጭቱ በተለያዩ ምክንያቶች ድምፅ የማይሰጥባቸውን 32 የምርጫ ጣቢያዎች እንደማይጨምር ጠቅሰዋል።

በዞኑ ከ1 ሚሊየን 18 ሺህ በላይ መራጮች ተመዝግበዋል።

በአፈወርቅ እያዩ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.