Fana: At a Speed of Life!

በኢትዮጵያ ላይ የሚደረገውን ጫናና ጣልቃ ገብነት የሚቃወም ሰልፍ በብራስልስ ተካሄደ

 

አዲስ አበባ፣ህዳር 7፣2014 (ኤፍ ቢሲ) በኢትዮጵያ ላይ የሚደረገውን አሉታዊ አለም አቀፍ ጫናና ጣልቃ ገብነት በመቃወም በብራስልስ ከተማ በአውሮፓ ህብረት ቢሮ ፊት ለፊት ሠላማዊ ሰልፍ ተካሄደ።

የአውሮፓ ህብረት በሀገራችን ላይ የሚያደርገውን ያልተገባ ጫና በመቃወም በበርካታ መቶዎች የሚቆጠሩ ከቤልጂየም፣ ከሉግዘምበርግ ፣ከሆላንድ ፣ከፈረንሳይ፣ ከጀርመን ፣ከስዊዘርላንድ ፣ከጣሊያን እና ከስፔይን የተወጣጡ ኢትዮጵዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን እንዲሁም የኢትዮጵያ ወዳጆች በተገኙበት በአውሮፓ ኮሚሽን ፊት ለፊት የተቃውሞ ሰልፍ አካሂዷል:: የዪናይትድ ስቴስ ጣልቃ ገብነትና ጫናንም ተቃውመዋል።

ሰልፉ በቤልጂየም በሚገኙ የዳያስፖራ አድቮኬሲ ቡድን የተዘገጃ ሲሆን፣ አውሮፓ አቀፍ ለማድረግ ከየአገሮቹ የተውጣጣ ጊዜያዊ አስተባባሪ ኮሚቴ በማዋቀር ሠፊ ዝግጅት የተደረገ መሆኑ ታውቋል::

በተቃውሞ ሰልፉ ላይ የተለያዩ መፈክሮች እና ፖሰተሮች የቀረቡ ሲሆን ፣ ከተለያዩ የአውሮፓ አገሮች የተገኙ የዳያስፖራ ማህበረሰብ ተወካዮች እና ወዳጆች ጭምር መልእክት ማስተላለፈቸው ተገልጿል፡፡

በሠልፉ አዘጋጆች በጽሑፍ የተዘጋጀውንም ደብዳቤ ከአውሮፓ ኮሚሽን የውጭ ግንኙነት አገልግሎት ተወካይ በሰልፉ ቦታ ተገኝተው መቀበላቸው መታወቁን ከውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.