አቶ አወል አርባ ከዴንማርክ የልማት ትብብር እና የዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ፖሊሲ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፣ ጥር 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ከዴንማርክ የልማት ትብብር እና የዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ፖሊሲ ሚኒስትር ዳን ጆርገንሰን ጋር ተወያዩ፡፡
በውይይታቸውም በግጭት ምክንያት የወደሙ አካባቢዎችን መልሶ ማቋቋም በሚቻልበት ላይ መምከራቸውን የክልሉ መገናኛ ብዙኃን ዘግቧል፡፡
ዳን ጆርገንሰንና ልዑካቸው አፋር ክልልን በመጎብኘት ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ለመረዳት እንደሚስያችላቸው ገልጸዋል፡፡