ጠ/ሚ ዐቢይ የአረንጓዴ ዐሻራ የችግኝ ተከላ ቅድመ ዝግጅትን በተመለከተ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተወያዩ
ችግኝት መትከልን እንደዘመቻ ስራ ሳይሆን ኑሮ ዘይቤ ማድረግ ይገባል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።
ለችግኝ ተከላው ከቅድመ ዝግጅት እስከ ተከላ 600 ሚሊየን ብር ወጪ እንደሚደረግ ተገልጿል።
በመጪው የክረምት ወራት 1 ነጥብ 7 ሚሊየን ሄክታር መሬት ላይ የችግኝ ተከላ እንደሚካሄድ የሚጠበቅ ሲሆን ለዚህ የሚያስፈልገው 84 በመቶ ችግኝ መፅደቁ ተነግሯል።
በአላዛር ታደለ