ሰላማችንን እየጠበቅን በምርጫው ላይ መሳተፍ ይገባናል – የአፋር ህዝቦች ፓርቲ ሊቀመንበር
አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 14 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ሰላማችንን እየጠበቅን በምርጫው ላይ መሳተፍ ይገባናል ሲሉ አቶ ሙሳ አደም የቀድሞው የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ እና የአፋር ህዝቦች ፓርቲ ሊቀመንበር ገለጹ።
አቶ ሙሳ አደም÷ “ሀገር ለዛሬ ብቻ የምንፈልጋት አይለችምና ሕዝቡ ሰላሙን በመጠበቅ በተረጋጋ መንፈስ የሚወክለውን ፓርቲ መምረጥ ይጠበቅበታል” ሲሉ ተናግረዋል።
የምርጫው ሂደት እስካሁን ሰላማዊ መሆኑን የገለጹት አቶ ሙሳ÷ የምርጫ ካርድ የወሰዱ ዜጎች በምርጫው ላይ እየተሳተፉ መሆኑን ተመልክቻለሁ ብለዋል።
ሁላችንም የራሳችንን አስተዋፅኦ ማበርከት በምንችልበት በዚህ ምርጫ ላይ በንቃት መሳተፍ አለብን ሲሉም ጥሪ ማስተላለፋቸውን ኢቢሲ ዘግቧል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
23,445
People Reached
326
Engagements
+1.2x Average
Distribution Score
Boost Post
207
2 Comments
7 Shares
Like
Comment
Share