Fana: At a Speed of Life!

የጸጥታ አካላት የደንብ ልብስን በሀገር ውስጥ በማምረት 60 ሚሊየን ዶላር ማዳን ተቻለ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የጸጥታ አካላት የደንብ ልብስን በሀገር ውስጥ በማምረት 60 ሚሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን መቻሉን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡

ሚኒስቴሩ በሀገር አቀፍ ደረጃ የጸጥታ ተቋማት የአልባሳት አቅርቦት አፈጻጸም ላይ ከፌዴራልና ከክልል ባለድርሻ አካላት ጋር ተወያይቷል።

የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል በኢትዮጵያ ታምርት ሀገራዊ ንቅናቄ ከውጪ ይገቡ የነበሩ ያለቀላቸው ምርቶችን ጥራታቸውን በጠበቁ የሀገር ውስጥ ምርቶች በመተካት የእሴት ጭማሬውን 62 በመቶ ማድረስ መቻሉን ገልጸዋል።

የጸጥታ ተቋማት የደንብ ልብስ በሀገር ውስጥ በመተካት ሂደት ላይ እስካሁኑ ከ18ሺህ በላይ ዜጎች የስራ ዕድል ተፈጥሮላቸዋል ብለዋል፡፡

በምርቱ ላይ 18 ፋብሪካዎች የተሳተፉ መሆናቸውን እና 60 ሚሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን ተችሏል ማለታቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.