ሉሲዎቹ የናይጀሪያ አቻቸውን ዛሬ ያስተናግዳሉ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሎምፒክ ማጣሪያ ጨዋታ የኢትዮጵያ ሴቶች ብሄራዊ ቡድን ከናይጀሪያ አቻው ጋር በዛሬው እለት ጨዋታውን ያከናውናል፡፡
ሁለተኛው ዙር የመጀመርያ ጨዋታ ቀን 9:30 በአበበ ቢቂላ ስታዲየም እንደሚካሄድ ከኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ሉሲዎቹ ለማጣሪያ ጨዋታው ላለፉት ስድስት ቀናት አካላዊ እና ስነ ልቦናዊ ዝግጅት ሲያደርጉ መቆየታቸው የሚታወስ ነው፡፡