Fana: At a Speed of Life!

የኢትዮጵያ አየር መንገድ 10ኛውን የቦይንግ የጭነት አውሮፕላን አስገባ

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 28 ፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ 10ኛውን የቦይንግ (Boeing 777-200LR) የጭነት አውሮፕላን ማስገባቱን አስታወቀ፡፡

አየር መንገዱ ያስገባው ዘመናዊ የጭነት አውሮፕላን ባለሁለት ሞተርና ከ100 ቶን በላይ ጭነት የመሽከም አቅም ያለው ነው ተብሏል።

የአየር መንገዱ አውሮፕላኖች የምዝገባ መለያ በ’A’ ፊደል ይጀምር የነበረ ሲሆን የአዲሱ አውሮፕላን ምዝገባ መለያ ግን በB በመጀመር እና ET-BAA የሚል ስያሜን በመያዝ አዲስ የአውሮፕላን ምዝገባ ምዕራፍ መክፈቱንም ነው አየር መንገዱ ያስታወቀው።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- hFBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.