Fana: At a Speed of Life!

15ኛው ከተማ አቀፍ የኪነ-ጥበብ ፌስቲቫል እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ የካቲት 15፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) 15ኛው ከተማ አቀፍ የኪነ-ጥበብ ፌስቲቫል በጊዮን ሆቴል በይፋ ተከፍቷል፡፡

ፌስቲቫሉ ”ኢትዮጵያዊነት የሥነ-ጥበብ ምናብ ሠረገላ ፣ የወል ትርክት አለላ” በሚል መሪ ቃል ነው እየተካሄደ የሚገኘው።

በፌስቲቫሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ፣ ታላላቅ የጥበብ ባለሙያዎች ፣ ታዋቂ ሰዎች ፣ወጣትና ህፃናት የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎችን ጨምሮ በርካታ የማህበረሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል፡፡

በፌስቲቫሉ የተለያዩ የኪነ-ጥበብ ስራዎች ለህዝብ ዕይታ እየቀረቡ ነው።

የአዲስ አበባ ባህል ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ሂሩት ካሳው (ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት ÷ብዝሃነታችንን ጠብቀንና አክብረን ኢትዮጵያዊነትን ከፍ ለማድረግ የኪነጥበብን ሚና መጠቀም ይኖርብናል ብለዋል።

በአዲስ አበባ ከተማ ለኪነ ጥበብ ዘርፉ የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በማካሄድ የኢትዮጵያዊነት ልዕልና በኪነ- ጥበቡ እንዲንፀባረቅ እየተሰራ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡

ፌስቲቫሉ ከዛሬ ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት እንደሚካሄድም ተጠቁሟል፡፡

በመለሰ ምትኩ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.