Fana: At a Speed of Life!

የፌዴራል መንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተለያዩ ክልሎች የተከናወኑ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የፌዴራል መንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ልዑክ በተለያዩ ክልሎችና ከተማ አሥተዳደሮች የተከናወኑ የልማት ሥራዎችን ተመለከተ።

መንግስት በሁሉም ክልሎች ያሉ ሃብትና ጸጋዎችን በአግባቡ ለመጠቀም እንዲቻል፣ የሚነሱ ቅሬታዎችንም ከኀብረተሰቡ ጋር ተቀራርቦ ለመፍታት ስራዎችን እያከናወነ መሆኑ ተገልጿል፡፡

የፌደራል ከፍተኛ አመራሮችም በተለያዩ ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች እያደረጉት ያለው የመስክ ምልከታና ድጋፋዊ ክትትል መርሐ-ግብር የዚህ ተግባር አካል መሆኑ ተጠቁሟል።

አመራሮቹ በጉብኝታቸው÷ የበጋ መስኖ ሥንዴ ልማት፣ የተፈጥሮ ሐብት ልማትና ጥበቃ ሥራ፣ የሌማት ትሩፋት፣ የሥራ ዕድል ፈጠራና ሌሎች የልማት ሥራዎችን ተመልክተዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.