በበጋ መስኖ ስንዴ ከ2 ሚሊየን ሔክታር በላይ ሰብል ተሰበሰበ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 16፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በበጋ መስኖ ስንዴ በዘር ከተሸፈነው 3 ሚሊየን ሔክታር ውስጥ 2 ነጥብ 1 ሚሊየኑ መሰብሰቡን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
እስካሁን ከተሰበሰበውም 73 ነጥብ 9 ሚሊየን ኩንታል ምርት መገኘቱን የሚኒስቴሩ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈፃሚ ከበደ ላቀው ተናግረዋል፡፡
በአጠቃላይ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት 120 ሚሊየን ኩንታል ምርት ይገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅም አመላክተዋል፡፡
በዙፋን ካሳሁን