Fana: At a Speed of Life!

አቶ ደስታ ሌዳሞ ሕዝቡ “ጽዱ ጎዳና – ኑሮ በጤና” ንቅናቄን እንዲቀላቀል ጥሪ አቀረቡ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 22፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሲዳማ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ደስታ ሌዳሞ ሕዝቡ “ጽዱ ጎዳና – ኑሮ በጤና” ንቅናቄን እንዲቀላቀል ጥሪ አቀረቡ፡፡

አቶ ደስታ ንቅናቄውን በመቀላቀል 10 ሺህ ብር ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን÷ ሕዝቡም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተከፈተው የሂሳብ ቁጥር 1000623230248 ድጋፍ በማድረግ ንቅናቄውን እንዲቀላቀል ጠይቀዋል፡፡

ንቅናቄው ሰዎች በየመንገድ ዳሩ ከመጸዳዳት ወጥተው ንጽህናውን በጠበቀ ቦታ የመጸዳዳት ባህላቸውን እንዲያሳድጉ፣ ለዚህ ደግሞ ደረጃቸውን የጠበቁ መጸዳጃዎች እንዲሠሩ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋ መሆኑ ይታወቃል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.