አስተዳደሩ ከህዝቡ ጋር ተግባብቶና ተቀናጅቶ በመስራት በአጭርና በረጅም ጊዜ የሚፈቱ ችግሮችን ለይቶ እየሰራ ነው – ከንቲባ አዳነች አቤቤ
የብልፅግና ፓርቲ አዲስ አበባ ቅርንጫ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ መለሰ አለሙ በበኩላቸው÷ ኢትዮጵያውያን ወደ ብልፅግና በሚወስደው ትክክለኛ መንገድ ላይ መሆናችንን የተረዱ አካላት ለማደናቀፍ ዛሬም እንደ ትናንቱ ቢረባረቡም ሕዝባችንን ይዘን እንሻገረዋለን ብለዋል።
ብዝሃነታችንን ለመለያየት በሃይማኖት አክራሪነት፣ በብሄር ፅንፈኝነት እንዲሁም በሂደት እየተመለሱ የሚገኙ ሲንከባለሉ የመጡ ችግሮችን በማራገብ አገር ለማፍረስ የሚጥሩትን አፍራሽ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ማድረግ ይገባልም ብለዋል፡፡
በመድረኩ በሰላም፣ በኅብረ ብሄራዊ ወንድማማችነትና እህትማማችነትን መገንባት፣ የኑሮ ውድነትን ማቃለል፣ የስራ አጥነት ችግርን ለመቅረፍ የጋራ ጥረት ማድረግ፣ የመንግስታዊ አገልግሎት ችግሮችን በጋራ መፍታት ፣ የልማት ጥያቄዎችን መመለስና ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር፣ የሚዲያን አዎንታዊ ሚና የማጠናከር ጉዳዮች ላይ የተናጠልና የጋራ ሚና ለመወጣት የሚያስችል መግባባት ተፈጥሯ መባሉን ከአዲስ አበባ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡