Fana: At a Speed of Life!

ለባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ግንባታ ማጠናቀቂያ ከ900 ሚሊየን ብር በላይ ተፈቀደ

 

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ለባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ግንባታ የቀሪ ሥራዎች ማጠናቀቂያ ከ900 ሚሊየን ብር በላይ መፈቀዱን የክልሉ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ገልጿል።

የቢሮው የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ምስክር ሰውነት ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር በነበራቸው ቆይታ ÷የማጠናቀቂያ ስራ ስታዲየሙ ዓለም አቀፍ ጨዋታዎችን ወደ ማስተናጋድ እንዲመለስ እንደሚያደርገው ገልጸዋል፡፡

የሁለተኛው ዙር ግንባታ በተያዘው የበጀት ዓመት መጨረሻ ለማጠናቅ እቅድ መያዙም ተመላክቷል።

የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) በጥቅምት ወር 2014 ዓ.ም የባህር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም መመዘኛ መስፈርቶችን ባለማሟላቱ ምክንያት ዓለም አቀፍ ጨዋታዎችን እንዳያስተናግድ ማገዱ ይታወሳል።
በወርቅነህ ጋሻው

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.