Fana: At a Speed of Life!

 ኢትዮጵያ ሁለት የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ ውድድሮችን እንድታስተናግድ ተመረጠች

አዲስ አበባ፣ የካቲት 15፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ ሁለት የምስራቅ እና መካከለኛው አፍሪካ ውድድሮችን እንድታስተናግድ በምስራቅ እና መካከለኛው አፍሪካ እግር ኳስ ማህበር ተመርጣለች፡፡

የምስራቅ እና መካከለኛው አፍሪካ እግር ኳስ ማህበራት ምክር ቤት ዛሬ በኬኒያ ባደረገው ጉባኤ ነው ኢትዮጵያ ውድድሮችን እንድታስተናግድ መመረጧን ያስታወቀው፡፡

በዚህም መሰረት ኢትዮጵያ የሴካፋ የሴቶች እግር ኳስ ሻምፒየንስ ሊግ እና ከ20ዓመት በታች ሴቶች ውድድሮችን ታስተናግዳለች።

ዩጋንዳ ከ 17 ዓመት በታች ወንዶች የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያን ታንዛኒያ የአፍሪካ ከ20 ዓመት በታች ወንዶች ማጣሪያ እና ዛንዚባር የሴካፋ ዋናውን ውድድር እና የአፍሪካ ትምህርት ቤቶች ማጣሪያ እንዲያስተናግዱ የተመረጡ አገራት ናቸው።

በወርቅነህ ጋሻሁን

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.