ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከኡጋንዳ ፕሬዚዳንት የተላከላቸውን መልዕክት ተቀበሉ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኡጋንዳ ፕሬዚዳንት ካጉታ ሙሴቬኒ የተላከላቸውን መልዕክት ተቀበሉ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ ከሠዓት በኋላ ከኡጋንዳ ሪፐብሊክ የፍትሕ እና የሕገ መንግሥታዊ ጉዳዮች ሚኒስትር ኖርበርት ማኦ ጋር ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸውም÷ በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው የገለጹት፡፡
በዚሁ ወቅትም ከኡጋንዳ ፕሬዚዳንት ካጉታ ሙሴቬኒ የተላከላቸውን መልዕክት መቀበላቸውን ገልጸዋል፡፡